Quick Links
- ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የክብር አምባሳደር ሆኖ ተሰየመ:
- ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በአዲሱ ዓመት የማስትሬት ፕሮግራሞችን ሊያስተዋውቅ ነው
- Economic Activities in Hawassa
- ንግድ ባንክ የበጀት ዓመቱ ክንውን አመርቂ መሆኑን ገለጸ
- የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በዓመቱ ውስጥ ግማሽ ቢሊየን ብር ማትረፉን ገለፀ
- የሀዋሳ ዪኒቨርስቲ ምሩቃን ሀገር አቀፍ ፈጠራ ተሸላሚዎች
- National Technology Roadmap
- አዲሷ አለም አቀፍ የቡና ቢዝነስ ተፅዕኖ ፈጣሪ
- የ2008 , የ300 ሺሕ ብር ፈጣሪዎች
- ከመስከረም 2009 ጀምሮ በ7.5 ሚሊየን ዶላር ሰብል የማዳቀል ስራ ሊጀመር ነው
- 400 ሺሕ ሰዎችን ለመቅጠር የሚያስችሉ ፓርኮች፣ በአማራ፣ በአሮሚያ፣ በደቡብና በትግራይ ክልሎች ሊገነቡ ነው
- የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 7ኛ የሆነው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ግንባታውን ጀመረ
- የአተት በሽታን ለመከላከል ትኩረት ሚሹ ጉዳዮች
- የመንጃ ፈቃድ አሰጣጥ ወደ ቀድሞ ቦታው ሊመለስ ነው
- አዲሱ የፌስቡክ የአይነስውራን ቴክኖሎጂ
- Tourist Facilities in Hawassa
- Ethiopian Airlines Career/Training Opportunities
- Hospitality and Hotels Ranking in Ethiopia
- Blessed Coffee Wins Start Up Africa Entrepreneurship
- Hawassa 2014 Livestock Investment Forum
- Hawassa City Background
- Amora Gedel Fish Market
- Experience Hawassa
- Foundation of Hawassa City
የአተት በሽታን ለመከላከል ትኩረት ሚሹ ጉዳዮች
በክልሉ ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ እንዳሻው ሽብሩ በሽታው በሀዋሳ ከተማ ተከስቷል እየተባለ የሚወራው ሀሰት መሆኑን ገጸው አዲስ አበባ ሄዶ የተመለሰ አንድ ግለሰብ በዚህ በሽታ ተጠርጥሮ በአዳሬ ሆስፒታል በተዘጋጀ ጊዜያዊ የአተት በሽታ ሕክምና ማዕከል የሕክምና እርዳታ እንደተደረገለት እና ሌሎች ከአዲስ አበባ መጥተው በበሽታው የተጠረጠሩ ሶስት ሰዎችም ለህክምና ወደ ማዕከሉ መግባታቸውን አስረድተዋል፡፡
ከሌላ ቦታ በሚመጡ ታማሚዎች ምክንያት በሽታው በሀዋሳ ከተማ እንዳይሰራጭ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አቶ እንዳሻው አሳስበዋል፡፡ ለአተት በሽታ ጥንቃቄ እንዲረዳዎት የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሏቸው፡፡
ምልክቶች...
ድንገት የሚጀምር መጠነ ብዙ፣ ተከታታይና አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የሚከሰት ሲሆን፥ ከዚህም የተነሳ ከሰውነት ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችና ፈሳሽ በብዛት ስለሚወገዱ ከፍተኛ የሰውነት ድርቀት (የአይን መሰርጐድ፣ የአፍና የምላስ መድረቅ፣ እንባ አልባ መሆን፣ የሽንት መጠን መቀነስና የቆዳ መሸብሸብ) ያስከትላል።
የመከላከያመንገዶች...
በሽታውን በቀላሉ መከላከል የሚቻል ስለሆነ ከበሽታው ራስንና ቤተሰብን ብሎም አካባቢን ለመከላከል የግልና የአካባቢዉን ንጽህና በሚገባ መጠበቅ አስፈላጊ ነው።
የበሽታው ምልክት የታየበት ሰው ከተገኘ በአስቸኳይ በአቅራቢያ ወደሚገኝ ጤና ተቋም እንዲሄድና አስፈላጊውን ምርመራና ህክምና ማግኘት ይኖርበታል።
እንዲሁም፦
• ውሃ አፍልቶና አቀዝቅዞ መጠቀም
• በውሃ ማከሚያ መድሃኒት የታከመ ውሃ መጠቀም
• ምግብን በሚገባ አብስሎ በትኩስነቱ መመገብ
• የምግብ ዕቃዎች ንጽህና መጠበቅ
• መፀዳጃ ቤትን በአግባቡ መጠቀም
• እጅን ከመጸዳጃ ቤት መልስ፣ ምግብ ከማዘጋጀት በፊት፣ ምግብ ከማቅረብ በፊት፣ ምግብ ከመመገብ በፊት፣ ሕጻናትን ካጸዳዱ በኋላ፣ ሕጻናትን ጡት ከማጥባትና ከመመገብ በፊት አንዲሁም ለበሽተኛ እንክብካቤ ካደረጉ በኋላ በሣሙና በሚገባ መታጠብ
• ማናቸውንም ከቤት የሚወጣ ደረቅ ወይም ፈሳሽ ቆሻሻ ውሃን እንዳይበክል በአግባቡ በተመደበለት ስፍራ ማስወገድ
• በዚህ በሽታ የተያዘ ሰው በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም መውሰድ
• ከበሽተኛው ከሚወጣ ፈሳሽ ጋር ንክኪ ያላቸውን እቃዎችና ቦታዎችን በአግባቡ ማጽዳት፡፡
ምንጭ፡ የክልሉ ጤና ቢሮ እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት