Quick Links
- ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የክብር አምባሳደር ሆኖ ተሰየመ:
- ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በአዲሱ ዓመት የማስትሬት ፕሮግራሞችን ሊያስተዋውቅ ነው
- Economic Activities in Hawassa
- ንግድ ባንክ የበጀት ዓመቱ ክንውን አመርቂ መሆኑን ገለጸ
- የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በዓመቱ ውስጥ ግማሽ ቢሊየን ብር ማትረፉን ገለፀ
- የሀዋሳ ዪኒቨርስቲ ምሩቃን ሀገር አቀፍ ፈጠራ ተሸላሚዎች
- National Technology Roadmap
- አዲሷ አለም አቀፍ የቡና ቢዝነስ ተፅዕኖ ፈጣሪ
- የ2008 , የ300 ሺሕ ብር ፈጣሪዎች
- ከመስከረም 2009 ጀምሮ በ7.5 ሚሊየን ዶላር ሰብል የማዳቀል ስራ ሊጀመር ነው
- 400 ሺሕ ሰዎችን ለመቅጠር የሚያስችሉ ፓርኮች፣ በአማራ፣ በአሮሚያ፣ በደቡብና በትግራይ ክልሎች ሊገነቡ ነው
- የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 7ኛ የሆነው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ግንባታውን ጀመረ
- የአተት በሽታን ለመከላከል ትኩረት ሚሹ ጉዳዮች
- የመንጃ ፈቃድ አሰጣጥ ወደ ቀድሞ ቦታው ሊመለስ ነው
- አዲሱ የፌስቡክ የአይነስውራን ቴክኖሎጂ
- Tourist Facilities in Hawassa
- Ethiopian Airlines Career/Training Opportunities
- Hospitality and Hotels Ranking in Ethiopia
- Blessed Coffee Wins Start Up Africa Entrepreneurship
- Hawassa 2014 Livestock Investment Forum
- Hawassa City Background
- Amora Gedel Fish Market
- Experience Hawassa
- Foundation of Hawassa City
ከመስከረም 2009 ጀምሮ በ7.5 ሚሊየን ዶላር ሰብል የማዳቀል ስራ ሊጀመር ነው
ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን በኢትዮጵያ የአምስት የሰብል አይነቶችን የማዳቀል አሠራሮችን ለማሻሻል የሚያስችል ፕሮጀክት ከመስከረም 2009 ጀምሮ ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑ ተገለጸ ። ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ከኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር የፈጸመው ስምምነት እንደሚያመለክተው ፕሮጀክቱ ተግባራዊ የሚደረገው በአጠቃላይ በ7ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ሲሆን ለአምስት ዓመታት የሚቆይ ይሆናል ተብሏል ።
በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ዋቅጅራ ለዋኢማ እንደገለጹት፤ ፋውንዴሽኑና ኢንስቲትዩቱ ተባብረው ተግባራዊ በሚያደርጉት ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም በአገሪቱ ሲከናወን የነበረውን የበቆሎ፣ ማሽላ፣ቦሎቄ፣ ሽምብራና ስንዴ ምርጥ ዝርያዎች የማዳቀል ቴክኖሎጂዎችንና አሠራሮች ለማሻሻል ታቅዷል ።በፕሮጀክቱ 15 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ የግብርና ምርምር ተመራማሪዎች እንደሚሳተፉ የጠቆሙት ዶክተር አዱኛ ፤ የግብርና ተመራማሪዎችን እውቀትና ክህሎትን ከማዳበሩም በተጨማሪም በፕሮጀክቱ አማካኝነት የሚወጡ የግብርና ቴክኖሎጂዎች በፈጣን ሁኔታ ለተጠቃሚዎች በማዳረስ ምርታማነትን የሚያሳድግ መሆኑን አስረድተዋል ።
ለምርምር የተመረጡት የሰብል ዝርያዎች የተሻለ የምግብ ይዘት እንዲኖራቸው ማድረግ የፕሮጀክቱ ትኩረት መሆኑን ጠቁመው፤ የማዳቀል ቴክኖሎጂውንና አሠራሩን በማሻሻል የተሻሉ ምርጥ ዝርያዎችን ለተጠቃሚ አርሶ አደሩ እንዲዳረስ እገዛ ይኖረዋል ብለዋል ።ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መደረግ ሲጀመር በበቆሎ ሰብል የሚደረገው የማዳቀልና የምርምር ሥራውን በአገሪቱ የበቆሎ አምራችነት በሚታወቁት የምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ትኩረት ሠጥቶ እንደሚሠራ ዶክተር አዱኛ አመልክተዋል ።
በተጨማሪም የሽንብራ ምርምርና የማዳቀል ሥራ በቱሉ ቦሎ አካባቢ ፣ የማሽላ ሰብል ምርምርና የማዳቀል ሥራውን በምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ፤ ቦሎቄን በአገሪቱ የስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች እንዲሁም የስንዴ ምርምርን በአርሲና በባሌ አካባቢዎች በማተኮር ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ዶክተር አዱኛ አብራርተዋል ።የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከተለያዩ የውጭ የግብርና ምርምር አካላት ጋር በመሆን በሰብል ምርምር ብቻ 60 የሚደርሱ ፕሮጀክቶችን እያካሄደ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል ።
Source: http://www.waltainfo.com/news/editors_pick/detail?cid=56