Quick Links
- ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የክብር አምባሳደር ሆኖ ተሰየመ:
- ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በአዲሱ ዓመት የማስትሬት ፕሮግራሞችን ሊያስተዋውቅ ነው
- Economic Activities in Hawassa
- ንግድ ባንክ የበጀት ዓመቱ ክንውን አመርቂ መሆኑን ገለጸ
- የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በዓመቱ ውስጥ ግማሽ ቢሊየን ብር ማትረፉን ገለፀ
- የሀዋሳ ዪኒቨርስቲ ምሩቃን ሀገር አቀፍ ፈጠራ ተሸላሚዎች
- National Technology Roadmap
- አዲሷ አለም አቀፍ የቡና ቢዝነስ ተፅዕኖ ፈጣሪ
- የ2008 , የ300 ሺሕ ብር ፈጣሪዎች
- ከመስከረም 2009 ጀምሮ በ7.5 ሚሊየን ዶላር ሰብል የማዳቀል ስራ ሊጀመር ነው
- 400 ሺሕ ሰዎችን ለመቅጠር የሚያስችሉ ፓርኮች፣ በአማራ፣ በአሮሚያ፣ በደቡብና በትግራይ ክልሎች ሊገነቡ ነው
- የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 7ኛ የሆነው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ግንባታውን ጀመረ
- የአተት በሽታን ለመከላከል ትኩረት ሚሹ ጉዳዮች
- የመንጃ ፈቃድ አሰጣጥ ወደ ቀድሞ ቦታው ሊመለስ ነው
- አዲሱ የፌስቡክ የአይነስውራን ቴክኖሎጂ
- Tourist Facilities in Hawassa
- Ethiopian Airlines Career/Training Opportunities
- Hospitality and Hotels Ranking in Ethiopia
- Blessed Coffee Wins Start Up Africa Entrepreneurship
- Hawassa 2014 Livestock Investment Forum
- Hawassa City Background
- Amora Gedel Fish Market
- Experience Hawassa
- Foundation of Hawassa City
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በአዲሱ ዓመት የማስትሬት ፕሮግራሞችን ሊያስተዋውቅ ነው
እስካሁን በበረራ መስተንግዶ (ሆስተስ)፣ በፍሮንት ኦፊስ ኦፕሬሽን፣ በቲኬቲንግና በሪዘርቬሽን፣ በሆቴል ኦፕሬሽን፣ በኤርላይን ደንበኞች አያያዝ ዘርፎችና በሌሎችም ተያያዥ የአቪዬሽን ሙያዎች ተማሪዎችን ሲያሠለጥን ቆይቷል:: ከዚህ በላይ ወደፊት የመንገደኞች አውሮፕላን አብራሪዎችን (ኮሜርሺያል ፓይለትስ) ለማሠልጠን የሚያስችሉትን መዋቅሮች በመዘርጋት ላይ እንደሚገኝና፣ ምናልባትም በሚቀጥለው ዓመት ሥልጠናውን መስጠት ሊጀምር እንደሚችል አቶ ገዛኸኝ ብሩ፣ የናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ ዲን ለሪፖርተር ገለጸዋል:: የናሽናል አየር መንገድ አካል የሆነው ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በአቪዬሽን መስክ በልዩ ልዩ የአገልግሎት መስኮች የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን እያሠለጠነ ቆይቷል::
ሰሞኑን ለሦስተኛ ጊዜ በልዩ ልዩ የአቪዬሽን መስክ 285 ሠልጣኞችን አስመርቋል:: ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት በተካሄደ ሥነ ሥርዓት፣ 285 ተማሪዎች በዲፕሎማ ደረጃ ከዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር (IATA) ጋር በመተባበር የተሰጣቸውን ሥልጠና በማኅበሩ መሥፈርት ተፈትነው ከ90 በመቶው በላይ ዝቅተኛውን መሥፈርት በማሟላት በማለፋቸው መመረቃቸውን አቶ ገዛኸኝ አብራርተዋል:: ከዓለም አቀፉ ማኅበር በተጓዳኝ የእንግሊዙ ኢንስቲትዩት ኦፍ ማኔጅመንት ጋር በመሆን ሥልጠናዎችን እየሰጠ የሚገኘው ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ፣ በዚህ ዓመት ሁለት አዳዲስ የማስትሬት ዲግሪ ፕሮግራሞችን እንደሚያስተዋውቅ አቶ ገዛኸኝ ገልጸዋል::
ኬንያ ከሚገኘውና ከነባሩ ሞይ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሚሰጡት ኮርሶች ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት እንዲሁም አቪዬሽን ማኔጅመንት የተባሉ ሲሆኑ፣ ሁለቱም በማስትሬት ዲግሪ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ መሰጠት የሚጀመርባቸው የትምህርት ዘርፎች መሆናቸው ተገልጿል:: ኮሌጁ እስካሁን በሆቴል ማኔጅመንት እንዲሁም በቱሪዝም ማኔጅመንት መስክ ሥልጠና ሲሰጥ ቆይቷል:: ምንም እንኳ በዚህ ዓመት እንደማይጀምር የታወቀው የአብራሪዎች ሥልጠና፣ ምናልባት በሚቀጥለው ዓመት ሊጀመር እንደሚችል ከአቶ ገዛኸኝ ለመረዳት ተችሏል:: ከዚህ ባሻገር ግን በአቪዬሽን ሳይንስ፣ በአውሮፕላን ዲዛይን፣ በአውሮፕላን ጥገና፣ በኤሮናውቲካል ኢንጂነሪንግ እንዲሁም በኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ መስኮች በቅድመና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሥልጠና ለመስጠት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ኮሌጁ ይፋ አድርጓል::